በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የጤና ቢሮ መሠረታዊ መድህን አገልግሎት ተደራሽነት ላይ ትኩረት እየተደረገ ነው ብሎ ገልጿል። በዚህ ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ውስጥ 891 ሺህ ቤተሰብ ተጠቃሚ ሆነው ክልሉን ሕዝብ የ45 በመቶ ተጠቃሚ አድርጎታል።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የጤና ቢሮ በወልቂጤ ከተማ የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ አፈፃፀም ግምገማ አካሄደ። በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ስራዎች አበረታች ውጤት ተመልክቷል ተብሎ ተገለጸ።
የቢሮው ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ በሽታ መከላከልን በማጠናከር የጤና ተቋማት ግንባታ፣ አዲሱን የጤና ኤክስቴንሽን ፍኖተ ካርታና ጽዱ ኢትዮጵያን ተግባራዊ በማድረግ እና የእናቶችን የወሊድ ማቆያ ክፍሎችን ምቹ በማድረግ ውጤታማ ስራዎች መሰራታቸውን ጠቁመዋል።
የጤና መድህን አገልግሎት ተደራሽነት ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አንስተው በዚህ 891 ሺህ ቤተሰብ የጤና መድህን አባል በመሆን ክልሉን ሕዝብ የ45 በመቶ ተጠቃሚ አድርጎ ከባለፈው ዓመት የተሻለ አፈጻጸም ተመዝግቧል።
የእናቶች ና ጨቅላ ህፃናት ሞት ለመቀነስ በርካታ የንቅናቄ ስራዎች በመስራት በዘርፉ ውጤት ተመዝግቧል። በመንግስት የጤና ተቋማት የአገልግሎት አሰጣጥ፣ የግብ አቅርቦት ና የሰው ኃይል እጥረትን ለሟላት ከአጋር አካላት ጋር በቅንጅት መሥራት እንዳለበት ቢሮው ገልጸው የአገልግሎት ጥራት ላይ ትኩረት በማድረግ የታየውን ማስቀጠል ያስፈልጋል ብሏል።