የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት በሚያዚያ 30፣ 2018 ባካሄደው ጉባኤ የከንቲባ አዳነች አቤቤ ያቀረቧቸውን ሹመቶች እና 9 ነጥብ 94 ቢሊየን ብር ተጨማሪ በጀት በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።
በጉባኤው ላይ አቶ ሚሊዮን ማቲዎስ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የከተማዋ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ፣ አቶ አሰግደዉ ኃ/ጊዮርጊስ የወጣቶችና ስፓርት ቢሮ ኃላፊ እና አቶ ሰለሞን ዲባባ የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ተሹመዋል።
ተጨማሪው በጀት ከዚህ ውስጥ 8 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ለከተማ ሰራተኞች የደመወዝ ድጎማ ሲሆን 996 ሚሊየን ብሩ ለልማት ሥራዎች ይውላል። ከንቲባዋ በጉባኤው ላይ የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ የምርት አቅርቦትን ማሳደግ እና የንግድ ሰንሰለቱን ማሳጠር እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል።
በተጨማሪም በህገወጥ ተግባር ላይ ተሰማርተው የተገኙ 18 ሺህ 400 ነጋዴዎች ላይ እርምጃ መወሰዱን ገልጸዋል።