የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ፍላይዱባይ ወደ ሶማሊላንድ ለሚደረጉ በረራዎች የሶማሊያ ኢ-ቪዛ መስፈርት በሃርጌሳ እና በበርበራ አውሮፕላን ማረፊያዎች ላይ እንደማይሠራ አረጋግጠዋል። ተሳፋሪዎች በመድረሻ ቪዛ ማግኘት ይችላሉ። ይህ የሶማሊያ የኢሚግሬሽን ስርዓት ደህንነት ተግዳሮቶች በኋላ ተወስዷል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ፍላይዱባይ የጉዞ መመሪያዎቻቸውን በማዘመን የሶማሊያ የኤሌክትሮኒክስ ቪዛ (ኢ-ቪዛ) መስፈርት በሃርጌሳ እና በበርበራ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያዎች ላይ እንደማይሠራ በይፋ አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ እንዳስታወቀው “የሶማሊያ የኢ-ቪዛ መስፈርቶች ወደ በርበራ ወይም ሃርጌሳ ለሚመጡ ተሳፋሪዎች አይሰራም” በማለት ገልጿል። ተሳፋሪዎች ወደ ሶማሊላንድ ሲደርሱ ቪዛ ማግኘት ይችላሉ ተናግሯል።
ፍላይዱባይ በተመሳሳይ የጉዞ ማስጠንቀቂያውን በማሻሻል መንገደኞች በሃርጌሳ እና በበርበራ ሲደርሱ ቪዛ ማግኘት ይችላሉ አረጋግጧል። ይህ እርምጃ ዓለም አቀፉ የአየር ትራንስፖርት ማህበር (IATA)ን ጨምሮ በርካታ አካላት የሶማሊላንድን የኢሚግሬሽን ቁጥጥር ከሶማሊያ ሥርዓት በመለየት የጉዞ መመሪያዎችን ካወጡ በኋላ ተወስዷል።
ይህ የተወሰደ የአሜሪካ መንግሥት በሶማሊያ የኢ-ቪዛ ሲስተም ላይ ትልቅ የደህንነት ጥሰት በኋላ ባወጣችው አስቸኳይ ማስጠንቀቂያ ነው። በሶማሊያ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ እንዳረጋገጠው ጠላፊዎች የሶማሊያን የኢ-ቪዛ መድረክ ሰብረው ቢያንስ 35,000 አመልካቾችን የግል መረጃ ተጋልጧል። ከዚህ መካከል በሺዎች የሚቆጠሩ የአሜሪካ ዜጎችን ጨምሮ ስም፣ የፓስፖርት ፎቶዎች፣ የትውልድ ቀኖች፣ የኢሜይል አድራሻዎች እና የመኖሪያ አድራሻዎች ይገኙበታል። የአሜሪካ መንግሥት የሶማሊያን ኢ-ቪዛ ሲስተም የተጠቀሙ ዜጎቹን በአስቸኳይ በአቅራቢያቸው የሚገኘውን ኤምባሲያቸውን እንዲያነጋግሩ እና ማንኛውንም አጠራጣሪ እንቅስቃሴ እንዲከታተሉ አሳስቧል።
ባለሞያዎች እንደሚሉት በሶማሊያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን እና በሱማሊላንድ መንግስት መካከል በአቪዬሽን ቁጥጥር ዙሪያ የሚታየው ውጥረት በሁለቱ አካላት ስልጣን ላይ የሚደረግ የፖለቲካ ትግል ማሳያ ነው። ለዚህ ውጥረት መነሻው የሶማሊያ አቋም መላውን የአየር ክልል የመቆጣጠር ስልጣን የእኔ ነው የሚል ሲሆን፣ ይህንንም ለማስፈጸም ወደ ሀርጌሳ ለሚጓዙ ሁሉም ተሳፋሪዎች የሶማሊያ ኢ-ቪዛ እንዲኖራቸው አዟል። በሌላ በኩል የሶማሊላንድ አቋም ደግሞ ራሷን የቻለች ሀገር በመሆኗ የአየር ክልሏን በሙሉ የመቆጣጠር መብት እንዳላት ትናገራለች። በዚህ መሠረት ዓለም አቀፍ አየር መንገዶች በሶማሊላንድ አየር ማረፊያዎች ከማረፋቸው በፊት ከራሱ የክልል ባለሥልጣናት የቅድሚያ ፈቃድ እንዲያገኙ በማዘዝ የሶማሊያን ኢ-ቪዛ ሕገ-ወጥ መሆኑን በመቃወም በአንድ ክልል ላይ የቁጥጥር ስልጣንን ለመጠየቅ የሚያደርጉትን ጥረት በተግባር እያሳዩ መሆኑ ተመላክቷል።