ኢትዮ ቴሌኮም በ2018 በጀት ዓመት 215.8 ቢሊየን ብር ገቢ አገኘ። ይህም የእቅዱን 99.7 በመቶ ማሳካት ሲሆን ከቀደመው ዓመት ጋር ሲነጻጸር 33.2 በመቶ ዕድገት አሳይቷል።
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ)። የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ በዛሬው ዕለት መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸው በበጀት ዓመቱ የገቢ ምንጭን በማስፋት በርካታ ሥራዎች መከናወናቸውን አብራርተዋል።
የተገኘው ገቢ የእቅዱን 99.7 በመቶ ማሳካት እንደተቻለ ተገልጿል። ከባለፈው ተመሳሳይ ዓመት ጋር ሲነጻጸርም 33.2 በመቶ ዕድገት ታይቷል።