የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ በ2018 በጀት ዓመት 29 ሚሊየን ሄክታር መሬት በማልማት 1.3 ቢሊየን ኩንታል ምርት መገኘቱን አስታወቁ።
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ)። የግብርና ሚኒስቴር እና ተቋማት ባለስልጣናት የግብርና ዘርፉን የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ገምግመዋል።
አቶ አዲሱ አረጋ እንዳሉት በምርት ዘመኑ 13 ሚሊየን ሄክታር በኩታ ገጠም መልማቱ ምርታማነትን አሳድጓል። ዘርፉ በአጠቃላይ 4.55 ቢሊየን ዶላር ገቢ አስገኝቷል፣ ከዚህም ቡና 3.1 ቢሊየን ዶላሩን ይሸፍናል።
መንግሥት የግብርና ግብዓት አቅርቦትን በማስተካከል 80 ቢሊየን ብር ድጎማ አድርጓል። በእንስሳት ሃብት ከ4.9 ሚሊየን በላይ እንስሳት በሰው ሰራሽ ዘዴ ተዳቅለዋል። በአረንጓዴ ዐሻራ ከ20 ሚሊየን በላይ ሰዎች ተሳትፈው ከ8 ቢሊየን በላይ ችግኞችን ተክለዋል።