በአማራ ክልል በ2018 በጀት ዓመት ከ36 ሺህ 665 ቶን ማር መመረቱ ተነገረ። ይህ ከታቀደው 33 ሺህ 333 ቶን በላይ ነው።
የክልሉ እንስሳትና ዓሣ ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ጋሻው ሙጨ ዶክተር ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንደተናገሩት የሌማት ትሩፋት መርሐ ግብር በንብ ማነብ ላይ መነቃቃት ፈጥሯል።
ዘመናዊ ቀፎዎች አቅርቦት እና የቅድመ ምርት ክትትል ለውጤቱ አስተዋጽኦ አድርገዋል። በተጨማሪም የገበያ ትስስር ለንብ አናቢዎች ጥቅም ለማረጋገጥ ጥረት እየተደረገ ነው።