በሳዑዲ ለሥራ የተሰማሩ ኢትዮጵያውያንን ደህንነት እና ጥቅም ለማስከበር እየተሰራ ነው

በሳዑዲ ዓረቢያ ለሥራ የተሰማሩ ኢትዮጵያውያን ደህንነት እና ጥቅም ለማስከበር በትኩረት እየተሰራ ነው። የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ከሳዑዲ የኢትዮጵያ አምባሳደር ጋር ተወያይታ ተደርጎ ነበር።

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) – በሳዑዲ ዓረቢያ ለሥራ የተሰማሩ ኢትዮጵያውያንን ደህንነት እና ጥቅም ለማስከበር በትኩረት እየተሰራ ነው።

የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በሳዑዲ ዓረቢያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሙክታር ከድር (ዶ/ር) እና ሌሎች የኤምባሲው አመራሮች ጋር ተወያይተዋል። በውይይታቸው በውጭ የሥራ ስምሪት እና በሳዑዲ ለሥራ የተሰማሩ ኢትዮጵያውያን መብት እና ጥቅም ማስከበር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መክረዋል።

አምባሳደር ሙክታር (ዶ/ር) በዚህ ወቅት በሳዑዲ ለዜጎች የሥራ እድል ለማመቻቸት ከተያዘው እቅድ አንጻር በተደረገው ስምምነት መሰረት ሰፊ የሥራ እድል እየተፈጠረ ነው ብለዋል። ለኢትዮጵያውያን ሙያተኞች በሳዑዲ የሥራ እድል በስፋት እንዲመቻች ከባለድርሻ አካላት ጋር የተጀመረው ውይይት ተጠናክሮ ይቀጥላል ነው ያሉት።

እድሉን አግኝተው ወደ ሳዑዲ የሚመጡ ዜጎች ደህንነታቸው ተጠብቆ የመጡለትን ዓላማ አሳክተው እንዲመለሱ በቁርጠኝነት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። ወ/ሮ ሙፈሪሃት በበኩላቸው ከታሪካዊና መልክዓ ምድራዊ ቅርበት እንዲሁም ካለው ሰፊ የሥራ እድል አንጻር ለሳዑዲ ዓረቢያ የሥራ ስምሪት ልዩ ትኩረት እንደተሰጠው ተናግረዋል።

የተያዘውን እቅድ ለማሳካት አስፈላጊው ድጋፍና ክትትል እንደሚደረግ መግለጻቸውን ኤምባሲው ለፋና ዲጂታል የላከው መረጃ ያመላክታል።

ይህ ድረ-ገጽ ኩኪዎችን ይጠቀማል

የእኛን ጣቢያ ለማሻሻል ለትንታኔ ኩኪዎችን እንጠቀማለን። የእኛን የሚስጥር ፖሊሲ አንብቡ የሚስጥር ፖሊሲ ለተጨማሪ መረጃ።
ውድቅ አድርግ