የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር ባለፉት አራት ዓመታት ሺዎችን ከሳይበር ጥቃት ተከላካይነት ወደ ፈጠራ ባለቤትነት ያሸጋገረውን የሳይበር ታለንት ቻሌንጅ በተመለከተ አዲስ መረጃ አስታውቋል።
ተቋሙ የአምስተኛው ዙር ሁለተኛ ዙር ፈተና ከሰኔ 12 እስከ ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ አስታውቋል።
የሳይበር ታለንት ዲቪዥን ኃላፊ ስመወርቅ እሸቱ እንዳሉት ዘንድሮ ከ14 ሺህ በላይ ሰልጣኞች ተመዝግበው ከ7 ሺህ በላይ የመጀመሪያውን ዙር ፈተና አጠናቅቀዋል።
የሁለተኛ ዙር ፈተናው በአዳማ፣ ደብረ ብርሃን፣ ባሕርዳር፣ ጅማ፣ ሀሮማያ እና ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲዎች የፊታችን አርብ እንደሚሰጥ ተገልጿል።
ከምስራቅ አፍሪካ ሀገራት፣ ከዩናይትድ አረብ ኤምሬቶች፣ ከአሜሪካ፣ ከእንግሊዝ እና ከደቡብ ኮሪያ አመልካቾች መቀበላቸው ተጠቁሟል።