ኢትዮጵያዊቷ የረጅም ርቀት ሯጭ የብርጓል መለሰ በድንገተኛ አደጋ ምክንያት በ36 ዓመቷ አረፈች። አትሌቷ ኢትዮጵያን በበርካታ ዓለም አቀፍ የጎዳና ላይ ውድድሮች በመወከል ሜዳልያዎችን አስገኝታለች።
የብርጓል መለሰ በፈረንጆቹ 2015 በኮንጎ ብራዛቪል በተካሄደው የመላው አፍሪካ ጨዋታዎች በግማሽ ማራቶን የነሐስ ሜዳልያ አግኝታለች። በዚያው ዓመት በቺካጎ ማራቶን የብር ሜዳልያ ተሸልማለች።
በፓሪስ ግማሽ ማራቶን ሁለት ጊዜ ድል የተቀዳጀች ሲሆን በሻንጋይ፣ ፕራግ እና ሂውስተን ማራቶኖችም በቀዳሚነት አጠናቅቃለች። በካናዳ በሚካሄደው የኦታዋ ማራቶን ለመሳተፍ ታቅዳ ነበር።
አትሌቷ ሚያዚያ 1982 ዓ.ም የተወለደች ሲሆን ግንቦት 4 ቀን 2018 ዓ.ም በጃን ሜዳ በድንገተኛ አደጋ ሞታለች። የቀብር ሥነ ሥርዓቷ ዛሬ ከምሽቱ 6 ሰዓት በመንበረ ጸባኦት ቅድስተ ሥላሴ ካቴድራል ቤተክርስትያን ይፈጸማል።