ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘገየ አስፋው ሕልፈት ኀዘናቸውን ገለጹ።
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ፕሬዚዳንቱ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት አቶ ዘገየ የኢትዮጵያ አርሶ አደሮች የዘመናት ፍትሃዊ ጥያቄ የሆነው መሬት ለአራሹ መልስ እንዲያገኝ በግንባር ቀደምትነት ጉልህ አስተዋፆኦ ያደረጉ ተራማጅ ሰው እንደነበሩ አስታውሰዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩም በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት አቶ ዘገየ የኢትዮጵያ አርሶ አደሮች በግፍ የተነጠቁት መሬት እንዲመለስላቸውና የመሬት ሥሪት እንዲቀየር ግንባር ቀደም ሚና እንደነበራቸው አውስተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተጨማሪም በተለያዩ ጊዜያት ሀገራቸውን በሚኒስትርነት ማገልገላቸውንና ህይወታቸው እስካለፈበት ጊዜ ድረስ የሀገራችንን ነባር ችግሮች በምክክር ለመፍታት በተቋቋመው ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነርነት ሲያገለግሉ እንደነበር ጠቅሰዋል።