ኢትዮጵያና ሶማሊያ መሪዎች በሁለትዮሽና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል። ትብብሩ ለሰላምና መረጋጋት አስተዋጽኦ እያደረገ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድና የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼኽ መሐሙድ በኢኮኖሚያዊ ትሥሥር፣ በሰላምና ደኅንነት እንዲሁም በቀጣናዊ መረጋጋት ላይ ተመካክረዋል።
ሁለቱ ሀገራት ድንበር፣ ቋንቋ፣ ባህል፣ እምነትና ወግ የሚጋሩ ቅርብ ጎረቤቶች ናቸው። የአሸባሪ ኃይሎችን ለመቀልበስ በተደረገው ጥረት ስኬት አስመዝግበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዛሬው ዕለት ባስተላለፉት መልዕክት የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት የህዝቦቻቸውንና መፃዒ መዳረሻቸውን እንደሚያካትት አመላክተዋል።