የጠቅላይ ሚኒስትሩ የደህንነት አማካሪ ሚኒስተር ዴዔታ ቀነዓ ያደታ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ ወደ ባሕር በር መመለስ በአፍሪካ ቀንድ ያለውን ሁለንተናዊ ትብብር ይበልጥ እንደሚያጠናክር ተናግረዋል።
ቀነዓ ያደታ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ቅድሚያ የሚሰጠው የሉዓላዊነት ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል። ጥያቄው በታሪክና በሕግ መሰረት ጠንካራ መሆኑን አመልክተዋል።
ይህ እንቅስቃሴ ብሔራዊ ጥቅምን የማረጋገጥ የህልውና ጉዳይ በመሆኑ ብሔራዊ አጀንዳ ሆኗል። ኢትዮጵያ በተለያዩ መድረኮች ጉዳዩን በፍትሃዊና በሰጥቶ መቀበል መርሕ ላይ በማተኮር እያስተዋወቀች መሆኑን ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ሠላም ለጎረቤት ሀገራት ሰላም ትልቅ ድርሻ እንዳለው ጠቅሰው የቀጣናውን ፖለቲካዊና ማህበራዊ ሁኔታ በመሠረታዊ መልኩ ማረጋጋት እንደሚቻል አስረድተዋል።