የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው በብልፅግና ፓርቲ መሪነት የተጀመሩ የሰላምና የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል።
ፓርቲው በሀድያ ዞን አመካ ወረዳ ጌጃ ከተማ ለተካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ እጩዎችን የማስተዋወቂያ መርሐ ግብር አካሂዷል።
እንዳሻው ጣሰው ፓርቲው ለሕዝብ የገባውን ቃል በተግባር እየፈጸመ መሆኑንና በልማት መስኮች የላቀ ውጤት እያስመዘገበ መሆኑን ገልጸዋል።
የሀድያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቲዎስ አኒዮ ደግሞ የአብሮነትና የትብብር እሴቶችን በማጠናከር ለጋራ ተጠቃሚነት ተግባራት እየተከናወኑ እንደሆነ አስታውቀዋል።