የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና የአርሶ አደሮችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ተናግረዋል።
የ2018/19 የመኸር እርሻ ንቅናቄ መርሐ ግብር በሀዋሳ ከተማ እየተካሄደ ነው።
አቶ ደስታ ሌዳሞ የግብርና ልማት ሥራዎች የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጡና ገበያን የሚያረጋጉ መሆናቸውን ገልጸዋል። ከበልግ ምርት ጎን ለጎን የመኸር ሰብልን ውጤታማ ለማድረግ በትኩረት እንደሚሰራም አስታውቀዋል።
የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ መምሩ ሞኬ ከ169 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች እንደሚለማ ተናግረዋል። ከ16.5 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅና ለዚህ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የርዕሰ መስተዳድሩ ጽ/ቤት ዳይሬክተር ቴዎድሮስ ታደሰ አስታውቀዋል።