የኦሮሚያ ክልል የእንስሳትና ዓሣ ሀብት ልማት ፕሮጀክት አምራቾችን በዘመናዊ አደረጃጀት በመደገፍ ከፍተኛ ስኬት እያስመዘገበ ነው።
የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ቶሌራ ደበላ እንዳሉት ፕሮጀክቱ የአመጋገብ ሥርዓትን ከማሻሻል ባሻገር በቤተሰብ ደረጃ የገቢ ምንጭን በከፍተኛ ሁኔታ አሳድጓል።
የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ደረጄ ጉደታ (ዶ/ር) ከአራት ሺህ በላይ አርሶ አደሮችን፣ ወጣቶችንና ሴቶችን በማደራጀት 2 ሺህ 118 የተሳካላቸው አምራቾችን ወደ ማሕበራት ማሳደግ መቻላቸውን ገልጸዋል። ማህበራቱ መሠረተ ልማት፣ መሣሪያዎችና ግብዓቶች ከተደረጉላቸው በኋላ ወደ ሥራ መግባታቸው ተገልጿል።
የፕሮጀክቱ ውጤት ከተጠበቀው በላይ መሆኑን ባለሥልጣናቱ ጠቁመዋል። ተሞክሮዎችን ወደ ሌሎች አካባቢዎች ለማስፋፋት እየተሠራ መሆኑም ተገልጿል።