የግብርና ሚኒስቴር በሩዝ ልማት የተመዘገበውን አስደናቂ ለውጥ ለማስቀጠል ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት እንዳለባቸው አስታወቀ።
የግብርና ሚኒስቴር በብሔራዊ ፍላጎት ፕሮግራም ደረጃ ከተያዘ ጀምሮ ያለውን የሁለት ዓመት ተኩል የሩዝ ዕቅድ አፈጻጸም ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ውይይት አካሂዷል።
በእርሻና ሆርቲካልቸር ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴዔታ ደሳለኝ ተሻለ በዚህ ወቅት ሩዝ በአስር ዓመቱ የግብርና መሪ ዕቅድ በትኩረት ሊሰራባቸው ከተለዩ የግብርና ምርቶች አንዱ መሆኑን ገልጸዋል።
በአነስተኛ አርሶ አደር በመኸር ሩዝ በ2012 ዓ.ም 60 ሺህ ሄክታር መሬት ይለማ ከነበረው በ2017 ዓ.ም ወደ 1.7 ሚሊየን ሄክታር ከፍ ተደርጓል። ምርቱም ከ1.8 ሚሊየን ኩንታል ወደ 62.9 ሚሊየን ኩንታል አድጓል።
ከውጭ የሚገባው ሩዝ ከ13.1 ሚሊየን ኩንታል ወደ 4.4 ሚሊየን ኩንታል ቀንሷል። በዚህም 442 ሚሊየን ዶላር ማዳን ተችሏል።