የመደመር መንግሥት ኢትዮጵያን በፈጣን የዕድገት ጎዳና ላይ ለማቆየት የተለያዩ ግዙፍ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎችን እያደረገ ነው።
መንግሥት የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጨምሮ ትላልቅ ፕሮጀክቶችን አጠናቋል። የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ እና የከተማ ማዘመኛ ፕሮጀክቶችም በተግባር ተተግብረዋል።
የንግድ ሕግ ከ60 ዓመታት በኋላ ተሻሽሏል። የባንክ እና የካፒታል ገበያ ዘርፎች ለውድድር ተከፍተዋል። በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ሀገሪቱ በምግብ እራሷን እንድትችል አድርጓታል።
በ2017 በጀት ዓመት የ9.2 በመቶ ዕድገት ተመዝግቧል። በአሁኑ ዓመት ዕድገቱ ከ10.2 በመቶ በላይ እንዲሆን ጥረት እየተደረገ ነው። በ30 ቢሊየን ዶላር የሚገነቡት ሰባቱ የጉባ ብሥራቶች ፕሮጀክቶች በተግባር ገብተዋል።