የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ባለፉት አራት ዓመታት በኢትዮጵያ የመሰረተ ልማት ፍትሐዊ ተደራሽነት ላይ አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ)።
በአንዳንድ ክልሎች የውሃ ሽፋን 38 በመቶ ብቻ ሲሆን በሌሎች እስከ 70 በመቶ ይደርስ እንደነበር ሚኒስትሩ አስታውሰዋል። ከለውጡ በኋላ ልማት ስራዎች በፍትሐዊ መንገድ ተደራሽ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በአፋር፣ በሶማሌ ክልሎች እና በቦረና ዞን የተጨባጭ ለውጦች መገኘታቸውን አንስተዋል። በቦረና አርብቶ አደሮች ወደ አርሶ አደርነት እየተቀየሩ ሲሆን በአፋር የተንዳሆ ግድብ ለመኖ ልማት ተጠቅሟል።
የሀገሪቱ የኃይል ማመንጨት አቅም ከ4 ሺህ ሜጋ ዋት በታች ከነበረው ወደ 10 ሺህ ሜጋ ዋት እየተጠጋ ነው። ይህ እድገት ኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ ጉባዔዎችን ለማስተናገድ እድል ፈጥሯል ሲሉ ሚኒስትሩ ተናግረዋል።