የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር በኢትዮጵያ የገጠር አካባቢዎች የሶላር ኤሌክትሪክ ሃይል ተጠቃሚነትን ለማሳደግ በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን አስታወቀ።
የዩኤንዲፒ አፍሪካ ሚኒ ግሪድ ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ ይመስላል ተፈራ እንዳሉት በበርካታ የገጠር አካባቢዎች የኤሌክትሪክ ሃይል ተደራሽነት ዝቅተኛ ነው።
ፕሮጀክቱ በኦሮሚያ፣ ሶማሌ እና ትግራይ ክልሎች ሶላር ሚኒግሪዶችን በመትከል ተደራሽነትን ለማስፋት እየሰራ ነው። ውጤታማነቱ ታይቶ ወደ ሌሎች አካባቢዎች ለማስፋት ታቅዷል።
የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ የቀደሙትን የመንግሥት ብቻ ፕሮጀክቶችን ይተካል። ባለሃብቶች እና ባንኮች ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል። የባለድርሻ አካላት የአቅም ግንባታ ሥልጠናም ተሰጥቷል።