የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወል አርባ መንግሥት የማኅበረሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትና የኑሮ ዘይቤ ለማሻሻል በልዩ ትኩረትና ቁርጠኝነት እየሰራ ነው ብለዋል።
አቶ አወል አርባ ይህንን ያሉት ከመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ ጋር በመሆን በገቢ ረሱ ዞን ዱለቻና አሚበራ ወረዳዎች የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶችን ሲመርቁ ነው።
ፕሮጀክቶቹ ሴቶችና ሕፃናት ውሃ ለመፈለግ የሚያደርጉትን እንግልት በመቀነስ ለሕፃናት የትምህርት ጊዜ እንዲጠቀሙ አስችለዋል። እንዲሁም የውሃ ወለድ በሽታዎችን በመከላከል ጤናማ ሕይወት እንዲኖር አስተዋጽኦ ያደርጋሉ።
በተጨማሪም የመስኖ ፕሮጀክቶች አርብቶ አደሮች ከቦታ ቦታ መንቀሳቀሳቸውን በመቀነስ ወደ ከፊል አርሶ አደርነት የኑሮ ዘይቤ እንዲሸጋገሩ መሰረት ጥለዋል።