በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ግልገል በለስ ከተማ የክልሉ ማዕድን ሃብትና ግብርና ዘርፎች ትብብር ለማጠናከር የተደረገ ውይይት ተካሂዷል፡፡
የክልሉ ማዕድን ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ቱጃኔ አደም በውይይቱ ላይ እንደተናገሩት በክልሉ ያልተነካ እምቅ የማዕድን ሃብት አለ፡፡ ይህንን ሃብት በዘመናዊ መንገድ ለማልማት መንግሥት በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በዘርፉ የሚታዩ ሕገ ወጥ ተግባራትን ለመከላከል ኮሚቴ ተቋቁሞ እየተሰራ መሆኑንም አቶ ቱጃኔ አደም አመልክተዋል፡፡ የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊዎች ደግሞ የግብርና ሪፎርም ስራዎች ውጤት ማስገኘታቸውንና የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የተቀናጀ ስራ አስፈላጊነት አንስተዋል፡፡
የመተከል ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ መለሰ ኪዊ በበኩላቸው የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተቀናጀ የግብርና ሥርዓት መዘርጋት እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡