የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የተፈጥሮ ሃብትን ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ጋር ማጣመርና ማልማት እንደሚገባ ገልጿል።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሦስተኛው ዙር የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ፈጠራ ውድድር አውደ ርዕይና ፓናል ውይይት ተካሂዷል።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ (ዶ/ር) በዘርፉ ያሉ ፀጋዎችን ወደ ሃብት መቀየር እንደሚቻል ተናግረዋል። ወጣቶችን ስራ ፈጣሪ ለማድረግ የሚደረገው ጥረት መቀጠል እንዳለበትም አሳስበዋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አንተነህ ፈቃዱ በክልሉ በርካታ የፈጠራ ስራዎች መገኘታቸውን ገልጸዋል። 146 የፈጠራ ስራዎችና ቴክኖሎጂዎች በውድድሩ ቀርበዋል።