የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነፃነት በሚል መሪ ሃሳብ የተካሄደው ሀገር አቀፍ ጉባኤ በአዲስ አበባ ለሦስት ቀናት ተካሂዶ ተጠናቋል። ጉባኤው ከ30 ሺህ በላይ ተሳታፊዎችን በማሰባሰብ የመረጃ ልማት ስራዎችን አሳይቷል።
የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር በከር ሻሌ (ዶ/ር) እንደገለጹት ጉባኤው በአውደ ርዕይ መልክ የተሰሩ ስራዎችን እና ውጤቶችን አቅርቧል።
የመረጃ ልማት ስራዎች በሕብረተሰብ ጤና፣ በግብርና ጥናት፣ በቤተሰብ ወጪ ጥናት እና በድርጅት ቆጠራ በአራት ዘርፎች ተከናውነዋል። ይህ ስራ የሀገር አቀፍ የምርት እድገት ክለሳ ለማድረግ ይረዳል ተብሏል።
የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ በረከት ፍስሃጽዮን ጉባኤው ሕብረተሰቡ ስለ መረጃ ያለውን እውቀት ከፍ እንዳደረገ አመልክተዋል።