የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለምክክር ጉባኤ የተዘጋጁ አጀንዳዎችን ለፖለቲካ ፓርቲዎች በማቅረብ ግብዓት እየሰበሰበ ነው።
በአዲስ አበባ የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ እንደተናገሩት ኮሚሽኑ በአሁኑ ወቅት አጀንዳዎችን በመቅረጽ፣ በማደራጀትና በማጠናቀር ምዕራፍ ላይ ይገኛል።
በቅርብ ጊዜ ውስጥ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ለማድረግ በዝግጅት ላይ መሆኑን ጠቅሰው የፓርቲዎች ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ኮሚሽኑ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጀመሩትን ጥረት እንዲያጠናክሩ ጥሪ አቅርቧል።