የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ ሰለሞን አየለ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሕዝብ ድምፅ የኢትዮጵያ አሸናፊነት የሚበሰርበት ነው ሲሉ ተናግረዋል።
አቶ ሰለሞን አየለ እንዳሉት ምክር ቤቱ ከ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ ልምድ በመቀመር ለ7ኛው ስኬት እየሰራ ነው። ቅድመ ዝግጅትና የዲጂታል ዕጩዎች ምዝገባ በስኬት ተጠናቅቋል።
የምርጫ ተከታታይ ኮሚቴ በማቋቋም ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጋር ለሂደቱ አስቻይ ሁኔታዎችን እያጠኑ ነው። ከግንቦት 20 ጀምሮ የጥሞና ጊዜ በመሆኑ ፓርቲዎች ለምርጫ ሕጉ ተገዢ እንዲሆኑ አሳስበዋል።
በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት መራጮች ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ድምፅ ይሰጣሉ። መራጩ ሕዝብ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር እንዲያረጋግጥ ጥሪ ተደርጓል።