የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ሊቀመንበር በለጠ ሞላ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዲሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲከናወን የፓርቲው ሚና እንደሚወጣ አረጋግጠዋል።
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ በአዲስ አበባ የውይይት መድረክ አካሂዷል። በዚህ መድረክ ፓርቲው በቅድመ ምርጫ ዝግጅቶች እና በሀገራዊና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይቷል።
የፓርቲው ሊቀመንበር በለጠ ሞላ ዲሞክራሲያዊ ምርጫ የህዝብን ተጠቃሚነት የሚያፀና መሆኑን ገልጸዋል። ዘላቂ ሰላም እና ልማት የፓርቲው ቀዳሚ አጀንዳዎች መሆናቸውንም አመልክተዋል።
አብን የፖሊሲ አማራጮቹን ለህዝቡ በማስተዋወቅ ላይ ይገኛል። ፓርቲው በምርጫ እና በድህረ ምርጫ ጉዳዮች ላይ ያለውን ሚና በተመለከተ ተወያይቷል።