ከ25 በላይ የኢትዮጵያ ሚዲያዎች በአዲስ አበባ ተገናኝተው የዴሞክራሲ ግንባታን ለማጠናከር እና ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ለማሳካት ተስማምተዋል።
የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ባወጣው መረጃ መሠረት በመድረኩ ተሳታፊዎች የዴሞክራሲ ልምምድን ለመቅረጽ፣ ለመግራት፣ ለማስፋት እና ለማጽናት የሚዲያው ዘርፍ ያለውን ሚና ተመልክተዋል።
በዚሁ ውይይት ላይ ሚዲያዎች በሀገር ብሔራዊ ጥቅሞች ላይ በትብብር እንዴት መሥራት እንዳለባቸው ተመካክረዋል። የግብዓት እና የሰው ኃይልን በማቀናጀት በጋራ ለመስራት ውል አስርተዋል።
የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ይህንን የታሪክ አጋጣሚ በመጠቀም ሀገርን በጽኑ መሠረት ላይ መገንባት እንደሚቻል አስታውቋል።