የፖለቲካ ሳይንስና የስነ አስተዳደር ምሁራን ነጻ፣ ፍትሐዊና ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ለሀገር ሰላምና ጠንካራ ኢኮኖሚ መሰረት መሆኑን አስረድተዋል።
በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ መምህር ሙላለም ኃይለማሪያም የህዝብ ፍቃድ መሰረት ያደረገ ምርጫ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገትን ያመጣል ብለዋል።
በጅማ ዩኒቨርሲቲ ዶክተር ፍቃዱ ቶሎሳ ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ለጋራ የሀገር ልማት ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት ገልጸዋል።
የስነ ዜጋ መምህር ሁስማን ቃሲም ከምርጫ በኋላ ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር የዲሞክራሲ መገለጫ እንደሆነ አመልክተዋል። ምሁራኑ ህዝቡ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በድምጹ ፍትሐዊ አስተዳደር ለሀገር እድገት አስተዋጽኦ እንዲያደርግ ጠይቀዋል።