የሕግ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ምሁራን ዜጎች በምርጫ የሚያደርጉት ንቁ ተሳትፎ ዴሞክራሲን ያጎለብታል ሲሉ ተናግረዋል።
በአዲስ አበባ የተካሄደው ውይይት ላይ የመንግሥት ምስረታ በምርጫ ሲሆን የሀገርን እድገት ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን አመልክተዋል።
የዓለም አቀፍ ሕግ ምሁር ዶክተር ተሻለ ሰበሮ የሀገር ውስጥ ጥንካሬ በተገቢ ሁኔታ ከተገነባ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተፅዕኖ ፈጣሪ ለመሆን እንደሚያስችል ገልጸዋል።
የሥራ አመራር አማካሪ አቶ ጌትዬ ትርፌ የዜጎች የምርጫ ሂደት ተሳትፎ ዴሞክራሲ እንዲጎለብት ያደርጋል ሲሉ ተናግረዋል። በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ መምህር አበራ ኤቢሶ ደግሞ ዴሞክራሲያዊ እድገት ላይ የደረሱ ሀገራት የህዝባቸውን ተሳትፎ በማሳደግ እንደተሳካላቸው አመልክተዋል።