የሐረርና ቆቦ ከተማ ነዋሪዎች ለሀገር ልማት ይበጃል የሚሉትን ፓርቲ በምርጫ ለመምረጥ ተዘጋጅተዋል።
የሐረር ከተማ ወጣቶች በምርጫው ዕለት ተገቢውን ፓርቲ ለመምረጥ ቁርጠኛ መሆናቸውን አስረድተዋል።
የቆቦ ከተማ ነዋሪዎች ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በቂ ዝግጅት ማድረጋቸውንና በምርጫ ካርዳቸው የመንግሥት ምስረታ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን እንደሚጠቀሙ ተናግረዋል።
ነዋሪዎቹ ሕዝብ የመንግሥት የመመሥረት መብቱን መጠቀም እንዳለበት አጽንዖት ሰጥተዋል።