የብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የምረጡኝ ቅስቀሳ አካሄደ። መርሐ ግብሩ በደብረ ማርቆስ፣ ፍኖተሰላም እና ሌሎች ከተሞች ተካሂዷል።
የብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ በአማራ ክልል የተለያዩ ከተሞች ዘመቻ አካሄደ። መርሐ ግብሩ በደብረ ማርቆስ፣ ፍኖተሰላም፣ አዴት፣ ግንደወይን፣ ፈለገ ብርሃን እና ደብረ ወርቅ ተካሂዷል።
ተሳታፊዎች የሀገርን ልማትና አንድነት የሚያጠናክሩ መልዕክቶችን አስተላልፈዋል። ወጣቶቹ ለብልጽግና ፓርቲ ያላቸውን ድጋፍ ገልጸው በተጀመሩ ጉዞዎች ስኬት የበኩላቸውን ሚና ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
በተጨማሪም ወጣቶች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት እንዲሳተፉ ተጠቁሟል። መርሐ ግብሩ በየአካባቢዎቹ የብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ አባላትና ደጋፊዎች ተሳትፈዋል።