የአማራ ክልል ሴቶች፣ ወጣቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ በዘንድሮ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት 8.6 ሚሊየን ዜጎች እንደሚሳተፉ አስታወቀ።
የቢሮው ኃላፊ ወ/ሮ ብርቱካን ሲሳይ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንደገለጹት አገልግሎቱ የወጣቶችን ሰብዕና ለመገንባትና ብሔራዊ አንድነትን ለማጠናከር ያተኩራል።
ከተሳታፊዎቹ መካከል 5.8 ሚሊየን ወጣቶች ናቸው። 15 ሚሊየን የማኅበረሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ እንደሚሆኑና 20 ቢሊየን ብር የመንግሥት ወጪ ለማዳን እቅድ መያዙን አመልክተዋል።
አገልግሎቱ ከሐምሌ 1 ቀን 2018 እስከ መስከረም 20 ቀን 2019 ዓ.ም ይካሄዳል። የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር፣ የቤቶች ግንባታና ማደስ እንዲሁም ትምህርታዊ ድጋፎችን ያካትታል።