የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከሐምሌ 8/2018 ዓ.ም ጀምሮ በሚካሄደው ጉባኤ 4 ሺህ ተወካዮችን ለመቀበል ዝግጅት አድርጓል።
ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር) እንደገለጹት ሂደቱ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል። የታጠቁ ኃይሎችን፣ ተፈናቃዮችን እና ከሀገር ውጪ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን ለማካተት ጥረት ተደርጓል።
ጉባኤው በተከባበረ መንፈስ ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል። ኮሚሽኑ ከጉባኤው በኋላ የሚወጡ ምክረ ሀሳቦችን በቅርበት ይከታተላል።
መስፍን አርዓያ ምክክር ሁሉንም አካል አሸናፊ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።