የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ከሐምሌ 8/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ሳምንታት በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ አስታወቀ።
ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር) ጉባኤው በመሰረታዊ አጀንዳዎች ላይ በሰለጠነ መንገድ በመነጋገር ለዘላቂ ሰላም ጽኑ መሰረት የሚጣልበት እንደሆነ ተናግረዋል።
የምክክር ሂደቱ በ12 ክልሎችና በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች አጀንዳ መሰብሰቡን ገልጸዋል። ተሳታፊዎች ጉባኤው ከመጀመሩ አንድ ሳምንት ቀደም ብለው በአዲስ አበባ እንዲገቡ ይደረጋል።
ኮሚሽኑ ሂደቱ ወደ ዋናው ምዕራፍ እየተሸጋገረ መሆኑን አመልክቷል። ሁሉም ባለድርሻ አካላት ድጋፋቸውን እንዲያጠናክሩ ጥሪ አቅርቧል።