የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሂደትን በተመለከተ 14ኛውን መደበኛ ጉባኤ በአዲስ አበባ አካሂዷል። ምክር ቤቱ የፖለቲካ ፓርቲዎች በዴሞክራሲ ግንባታ ውስጥ ያላቸውን ድርሻ አጽንዖት ሰጥቷል።
ግንቦት 12፣ 2018 በተካሄደው ጉባኤ ላይ ምክር ቤቱ የምርጫ ሂደቱ ነጻ፣ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ እየተከናወነ መሆኑን አመልክቷል። ፓርቲዎቹ በክልል፣ በዞኖችና በወረዳዎች ደረጃ መዋቅራቸውን እያሰፉ እንደሆነ ተገልጿል።
የክልሉ መንግሥትና ገዥው ፓርቲ ለምክር ቤቱ ስራዎች በጀት፣ ቢሮና ሎጂስቲክስ ድጋፍ እያደረጉ መሆኑ ተነስቷል። ፓርቲዎቹ ተፅዕኖ ሳይደረግባቸው እጩዎቻቸውን በማስመዝገብና አባላትን በማደራጀት እየሰሩ ናቸው።
የምክር ቤቱ ምክትል ሰብሳቢና የብልጽግና ፓርቲ ተወካይ አቶ ሞገስ ኢደኤ ፓርቲዎቹ በፉክክርና በትብብር ሂደቱን በሰላም ለማጠናቀቅ እየሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።