የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ውጤት ይፋ አድርጓል። ብልጽግና ፓርቲ 438 መቀመጫዎችን አሸንፏል። ኢዜማ በሀገር አቀፍ ደረጃ ቀዳሚ ተፎካካሪ ፓርቲ ሆኗል።
በኢትዮጵያ በተካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ብልጽግና ፓርቲ 438 መቀመጫዎችን አሸንፏል። የቦርዱ ምክብር ሰብሳቢ ተስፋዬ ንዋይ ውጤቱን ይፋ አድርጓል።
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ 13 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና 73 የክልል እና የከተማ ምክር ቤት መቀመጫዎችን በማግኘት በሀገር አቀፍ ደረጃ ቀዳሚው ተፎካካሪ ፓርቲ ሆኗል። ፓርቲው በብሔራዊ ጥቅሞች ላይ ከሁሉም የኢትዮጵያ ኃይሎች ጋር በትብብር እንደሚንቀሳቀስ ገልጿል።
ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ምርጫው አዲስ የፖለቲካ ልምምድ ስር እየሰደደ መምጣቱን አመልክተዋል። የአፍሪካ ኅብረት ምርጫው ለኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ታሪካዊ መሰረት ጥሎ አልፏል ብሏል።