የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከ1139 የምርጫ ክልል ውጤቶች 1008ቱ ወደ ማረጋገጫ ማዕከል መድረሳቸውን አስታውቋል።
የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ከ501 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ክልሎች 446ቱ እና ከ638 የክልል ምክር ቤት ክልሎች 562ቱ መድረሳቸውን ገልጸዋል።
ቀሪዎቹ 131 ውጤቶች በርቀትና በመንገድ ሁኔታ ምክንያት በጉዞ ላይ እንደሆኑ ተገልጿል። በተጨማሪም ቦርዱ በአጠቃላይ 22 የፀደቁ ውጤቶችን በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ እና በሶማሌ ክልሎች ይፋ አድርጓል።
በ120 የምርጫ ክልሎች ላይ ቅሬታዎች ቀርበዋል። የቦርዱ የሕግ ባለሙያዎች ቅሬታዎቹን እያጣሩ ሲሆን ውጤቶቹ ከተጣራ በኋላ አጠቃላይ ውጤት በይፋ ሊታወቅ እንደሚችል ተገልጿል።