በኢትዮጵያ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዜጎች በነቂስ ወጥተው ድምጻቸውን ሰጥተዋል። ታዛቢዎችና ተፎካካሪ ፓርቲዎች ሂደቱን ግልጽና ፍትሐዊ እንደሆነ ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዜጎች የጠላት ጩኸት ሳያስቆማቸው በነቂስ ወጥተው ድምጽ ለመስጠት መታየታቸውን አመሰገኑ። ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ በአዲስ አበባ ቂርቆስ ወረዳ 4 ድምጿን ሰጥታለች።
የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ ስፔሲዮዛ ዋንዲራ (ዶ/ር) ሂደቱ በተቀናጀ መንገድ እየተካሄደ መሆኑን አረጋግጠዋል። ተፎካካሪ ፓርቲዎች ደግሞ ሕዝቡ የሉዓላዊ ስልጣን ባለቤት መሆኑን በተግባር አሳይቷል ብለዋል።
በሆሳዕና ከተማ ሙሽሮች የሰርጋቸውን ቀን አቋርጠው ድምጽ ሰጥተዋል። የጌዴኦ አባ ገዳ ቢፎም ዋቆ በዲላ ከተማ ተገኝተው ድምጻቸውን ሰጥተዋል።