የአማራ ክልል ሚሊሻ ኃይል ከማህበረሰቡ ጋር በመተባበር ሰላምን በማስከበር ግንባር ቀደም እየተሳተፈ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ ገለጹ።
የአማራ ክልል ሚሊሻ ኮሚሽን የ30 ዓመታት የጀግንነት ታሪክን በሚል መሪ ሐሳብ በባሕር ዳር ከተማ የምስረታ በዓልና የእውቅና መርሐ ግብር አካሂዷል።
አቶ አረጋ ከበደ በዚህ ወቅት ሚሊሻው ለተበላሹ 30 ዓመታት የሕዝብና መንግሥት አደራን በመወጣት አኩሪ ታሪክ ሰርቷል ብለዋል።
እንዲሁም የጠላቶችን ሴራ ለማክሸፍ ከፌዴራልና ከክልሉ የጸጥታ ኃይሎች ጋር በመተባበር የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ እንደሆነ አስታውቀዋል።