የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ ሆለታ በሚገኘው ግቢ ውስጥ 71ኛ ዙር መተማ ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን እያስመረቀ ይገኛል።
የጦር ሀይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፣ የመከላከያ ትምህርትና ስልጠና ዋና መምሪያ ኃላፊ ጄነራል ይመር መኮንን እና የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ አዛዥ ብርጋዲየር ጄነራል ጌታቸው ሀብታሙ ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት ወታደራዊ አታሼዎች በምረቃ ሥነ-ሰርዓቱ ተገኝተዋል።
በስልጠናው ብልጫ ያመጡ ዕጩ መኮንኖች በፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የማዕረግ ማልበስ ሥነ ስርዓት ተካሂዷል። ብርጋዲየር ጄነራል ጌታቸው ሀብታሙ ተመራቂዎቹ የወሰዱት ስልጠና ሁለንተናዊ የአመራር ጥንካሬን የሚያጎለብት እና ማንኛውንም የሠራዊት ግዳጅ መወጣት የሚያስችል አቅም እንደሚሰጣቸው ተናግረዋል።
ከኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት በተጨማሪ ከተለያዩ ሀገራት የመጡ አፍሪካውያን ዕጩ መኮንኖችም ስልጠናቸውን አጠናቀው መመረቃቸውን ኢዜአ ዘግቧል።