የጦር ኃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄኔራል አበባው ታደሰ ሰሜን ምዕራብ ዕዝ ከታሪካዊ ጠላቶች ወይም ባንዳዎች ሊመጣ የሚችል ጥቃትን ለመመከት በቂ ዝግጁነት ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
ጄኔራል አበባው ታደሰ በሰሜን ምዕራብ ዕዝ የግዳጅ ቀጣና ተገኝተው ይህን አስተያየት ሰጥተዋል። ዕዙ የተቋሙን ግዳጅ በጀግንነት እየፈፀመ መሆኑን አመልክተዋል።
የሕወሓትን ወረራ በመመከት እና በአማራ ክልል ግጭት ለመፍጠር በተንቀሳቀሰው ፅንፈኛ ቡድን ላይ ጠንካራ ርምጃ በመውሰድ ዕዙ ትልቅ ሚና ተጫውቷል ብለዋል። ለሠራዊት አባላቱም የአባቶቻቸውን ጀግንነት ታሪክ በመቀበል ኢትዮጵያን ለመጪው ትውልድ ማስረከብ እንዳለባቸው አሳስበዋል።
የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ በበኩላቸው ዕዙ ተደራራቢ ግዳጆችን በፅናት ፈጽሟል ሲሉ ለቀጣይ ተልዕኮዎች ዝግጁነቱ ከመቼውም ጊዜ በላይ መሆኑን አመልክተዋል።