የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የቀድሞ መቐለ ከንቲባ አታክልቲ ኃይለስላሴ በክልሉ የተፈጠረውን ሥርዓት አልበኝነት በተመለከተ አስተያየት ሰጥተዋል።
አታክልቲ ኃይለስላሴ ከፋና ፖድካስት ጋር ባደረጉት ቆይታ በትግራይ ክልል በቀድሞ አክራሪ የህወሓት ቡድን ምክንያት የዜጎች የደህንነት ስጋት እየጨመረ መምጣቱን ገልጸዋል።
እነርሱ እንደተናገሩት የቀድሞ ህወሓት ቡድን በፕሪቶሪያው ስምምነት መሠረት የታጣቂዎችን ትጥቅ የመፍታት ሒደት ሙሉ በሙሉ እንዳይተገበር እንቅፋት ሆኖ ቆይቷል። ይህም ታጣቂዎች ወደ ሰላማዊ ሕይወት እንዳይመለሱ አድርጓል።
በተጨማሪም የትምህርት ቤቶችና የጤና ጣቢያዎች የታጣቂዎች መሸሸጊያ ሆነዋል ሲሉ አመልክተዋል። የሰብዓዊ ድጋፎችም ለታለመላቸው ወገኖች እየደረሱ አይደለም ብለዋል።