የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ መዲናዋ ባለፉት አምስት ዓመታት የልማት አብዮት አካሂዳለች ሲሉ ተናገሩ። በባለፉት አስር ቀናት ውስጥ 11 ፕሮጀክቶችን ለአገልግሎት ክፍት ማድረጋቸውን አመለከቱ።
ከንቲባዋ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ኢንዱስትሪ ፓርኮችን፣ የመኖሪያ ቤቶችን፣ የህዝብ መዝናኛ ቦታዎችን እና የገበያ ማዕከላትን ጨምሮ የተከፈቱ ፕሮጀክቶችን ዘርዝረዋል። ለምሳሌ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ ከ20 ሺህ በላይ ዜጎችን የስራ እድል የሚፈጥር ሲሆን የላፍቶ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ የተደገፈ እንደሆነ ተገልጿል።
ከንቲባዋ አንዳንዶች እነዚህ ፕሮጀክቶች ለምርጫ ዓላማ እንደተከናወኑ ያነሳሉ ያሉት ሲሆን ነገር ግን ቀድሞ ያልተሰራ ስራ ለምርጫ ሊደርስ እንደማይችል አስታውቀዋል። ዋናው ህዝቡና ሀገር ተጠቃሚ እንዲሆን እንጂ ችግር እንደሌለው ተናግረዋል።
የተከፈቱት ፕሮጀክቶች በኢንዱስትሪ፣ መኖሪያ፣ መዝናኛ፣ ገበያ፣ ስፖርት፣ ትምህርት እና ጤና ዘርፎች ውስጥ ይገኛሉ። እነዚህም በተለያዩ ክፍለ ከተሞች እንደ ቦሌ፣ ለሚ ኩራ፣ አዲስ ከተማ እና ላፍቶ ተተግብረዋል።