የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በግሉ ዘርፍ የጤና ቱሪዝምን ለማሳደግ አበረታች ስራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ኒዩክለስ አጠቃላይ ሆስፒታል ዛሬ ለአገልግሎት ተከፍቷል።
ከንቲባዋ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ኒዩክለስ አጠቃላይ ሆስፒታል በህክምና ባለሙያዎች አክሲዮን ማህበር ተገንብቶ ለአገልግሎት መከፈቱን አስታውቀዋል።
ይህ ሆስፒታል በአዲስ አበባ የጤና ቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት ያጠናክራል ተብሏል። መንግስት ብቻ ሳይሆን በግሉ ዘርፍም ስራዎች እየተከናወኑ ናቸው።