ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በፋርማሲቲካል እና ሆስፒታል ዘርፎች የተገነባው አቅም በዓለም የመድኃኒት ቁጥጥር ኤጀንሲ እውቅና እንዳገኘ ተናገሩ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምላሽ ሲሰጡ የአገር ውስጥ የመድኃኒት ማምረት አቅም ከ4 በመቶ ወደ 44 እና 45 በመቶ እንደደረሰ ገልጸዋል።
በአዲስ አበባ ባለፉት ወራት በርካታ የሕክምና ተቋማት መመረቃቸውንና በሚቀጥሉት ወራት ተጨማሪዎች አገልግሎት እንደሚጀምሩ አመልክተዋል።
የወባ በሽታን ለመከላከል 3 ሚሊየን ቤቶች ጸረ ወባ ኬሚካል መረጨታቸውንና ለመጀመሪያ ጊዜ በ58 ወረዳዎች ክትባት መሰጠቱን አብራርተዋል።