ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከሩዋንዳ ከመጡ 128 የሕክምና ባለሙያዎች ጋር ማዕድ ቆርሰናል ሲሉ በማሕበራዊ ትስስር ገጻቸው አስታውቀዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ በልዩ የሕክምና ሥልጠና ላይ ከሚገኙ ከ400 በላይ የሕክምና ባለሙያዎች መካከል ከሩዋንዳ የመጡትን 128 ተቀብለዋል።
ባለሙያዎቹ የአፍሪካን የጤና ዘርፍ የወደፊት ፍላጎት ለማሟላት ከፍተኛ ዕውቀትና ብቃት ለማግኘት እየጣሩ መሆናቸውን ገልጸዋል። ተቋማትም ቀጣዩን የአፍሪካ ትውልድ በሕክምና ዘርፍ የመሪነት ሚና እንዲጫወት እያደረጉ መሆናቸውን አመልክተዋል።
በጋራ ዕውቀትና ዓላማ ይበልጥ ጤናማ የሆነች አፍሪካን መገንባት እንቀጥላለን ሲሉ አክለዋል።