ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚዲያዎች ለብሔራዊ ግቦች በቁርጠኝነት እንዲሠሩና የጋራ ማንነትን እንዲገነቡ አሳሰቡ።
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን በአዲስ አበባ በተካሄደው “የሚዲያ እመርታ ለትርክት ግንባታ” በሚል መሪ ሐሳብ በተዘጋጀው ሀገራዊ የምክክር መድረክ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተገኝተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በለውጡ ዓመታት የተደረጉ ሪፎርሞችን በመግለጽ የታሰሩ ጋዜጠኞች መፈታታቸውን፣ የጃሚንግ አሠራር ማቆሙን እና ሕጎች መሻሻላቸውን አመልክተዋል። ሚዲያዎች እውነትን በመዘገብ የተሳሳቱ ትርክቶችን ማስተካከል እንዳለባቸውም ገልጸዋል።
የናሽናል ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት፣ አዋሽ ኤፍ ኤም፣ ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን፣ ኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት፣ ኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን እና የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ተወካዮች በዘርፉ የተመዘገቡ ስኬቶችን አቅርበዋል።