ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መሪነት የፀጥታና ዴሞክራሲ ተቋማትን በማጠናከር ላይ ትገኛለች። ይህ ሪፎርም ለሀገር ጥንካሬና የዜጎች እኩል ተጠቃሚነት አስፈላጊ ነው።
ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ወደ ስልጣን መምጣት በኋላ የፀጥታና ዴሞክራሲ ተቋማት ሪፎርም ተከናውኗል። ተቋማቱ በአመራር፣ በቴክኖሎጂ እና በዴሞክራሲያዊ መሰረት የተጠናከሩ ሲሆን ለህግ ብቻ የቆሙ ናቸው።
የሆሚቾ ጥይት ፋብሪካ እና ስካይዊን ኤሮኖቲክስ ኢንዱስትሪ በመገንባት የመከላከያ ሠራዊትን ዘመናዊ ትጥቅ ማድረግ ተችሏል። በተጨማሪም የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ተቋቁሞ “ኤአይ ለሁሉም” በሚል ዩኒቨርሲቲ ለማቋቋም ስራ ተጀምሯል።
በብሔራዊ ምርጫ ቦርድና በፍትሕ አካላት ላይ የተደረጉ ሪፎርሞች ድንገተኛ የደኅንነት ክፍተቶችን ለመከላከል አስተዋጽኦ አድርገዋል።