የመከላከያ ትምህርትና ስልጠና ዋና መምሪያ ሃላፊ ጄነራል ይመር መኮንን እንዳሉት ለአሁናዊ የቀጣናችን ችግሮች ፈጣን ምላሽ የሚሰጥ ጠንካራ ተቋም ተገንብቷል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ የመከላከያ ኮሌጅ ዓመታዊ የብሔራዊ ደህንነት ኮንፈረንስ በአዲስ አበባ ተካሂዷል።
ጄነራል ይመር መኮንን ዓለም አቀፍ የደህንነት ሁኔታ እየተወሳሰበ መምጣቱን ጠቅሰው ብሔራዊ ጥቅምን ለማስጠበቅ ጠንካራ ተቋማት እንደሚያስፈልግ አጽንኦት ሰጥተዋል።
ብርጋዲየር ጄኔራል ጥላሁን ደምሴ የቀጣናዊ ስጋት ለመፍታት በሳል ዲፕሎማሲና ብሔራዊ ጥቅምን ማዕከል ያደረገ እቅድ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል።