የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ሀገርን ለማሻገር የማይወዛወዝ ምሰሶ ሆኖ ተልዕኮውን እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል።
ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ይህንን መልዕክት በማዕከላዊ ዕዝ መኮንኖች የግዳጅ አፈፃፀምና ቀጣይ አቅጣጫዎች መድረክ ላይ በበይነመረብ አስተላልፈዋል።
የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለመጠበቅ የተዘጋጀ ወታደራዊ አመራር ዓለም አቀፉዊ፣ አህጉራዊና ቀጣናዊ ጉዳዮችን በመረዳት የአሀድ ስነ ልቦናዊ ዝግጁነት ማረጋገጥ እንዳለበት አመልክተዋል።
የማዕከላዊ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ዘውዱ በላይ ተቋሙ በተለያዩ መስኮች የሚያሰለጥናቸው መስመራዊ መኮንኖች ከቴክኖሎጂ ጋር የሚግባቡ በመሆናቸው ተልዕኮን በአጭር ጊዜና አነስተኛ ኪሳራ የመፈፀም ብቃታቸው እየጨመረ መሆኑን ተናግረዋል።